አሁን የደረሰኝ መረጃ
.."አዲስ አበቤን የመንቀል ዘመቻ"
በአዲስ አበባ መሀል ከተማ ከፖስታ ቤት ጀርባ አራዳ ክ/ከተማ ወረዳ 01 ውጥረት ነግሷል። ኮሮና ቫይረስ አስቸኳይ አዋጅ ያላቆመው የዜጎች ሰቆቃ የታከለ ኡማ ቤት ፈረሳ ገደብ አጥቷል። አሁን በዚህ ጨለማ የከተማው አስተዳደር ባሰማራቸው አፍራሽ ግብረሃይል ብዛት ያለው ፖሊስ ወደ አካባቢዉ በማሰማራት ቤት በማፍረስ እቃቸዉን በአይሱዙ አስጭነዉ እየወሰደ መሆኑን ከደረሰን ጥቆማ ለማረጋገጥ ወደ አካባቢው ስልክ በመደወል ለማጣራት እንደቻልኩት ቤት የፈረሰባቸው ነዋሪዎች ጩኸትና ግርግር እንዳለ ለመታዘብ ተችሏል ። ግፈኛዉ የአዲስ አበባ ከተማ አስተዳደር ታከለ ኡማ በዚህ ወረርሽኝ አስቸኳይ አዋጅ አዲስ አበቤ የመንቀል ዘመቻ አጠናክሮ ቀጥሏል ህፃናት የያዙ እናቶች በምሽት ሜዳ ላይ ወድቋዋል።

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes