የሂልተን ሆቴል ጋዜጣዊ መግለጫ አፈና !
" ከደህንነት ተደውሎ ስለተነገረን አሁን መግለጫ መስጠት አትችሉም "
በዛሬው ዕለት ለሁለተኛ ጊዜ ሰናይ መልቲ ሚዲያ ምስረታና የአክሲዮን ሽያጭ፤ ይፋዊ መግለጫ መንግስታዊ አፈና በድጋሚ ተካሂዶበታል ።
ለአዲስ አበባ ሂልተን ሆቴል በቀን 27/ግንቦት/2011 ዓ.ም በተፃፈ ደብዳቤ ፤ "ጌት አማካሪዎች" የንግድና ኢንቨስትመንት ማማከር ድርጅት፤ የሰናይ ቲቪ ምስረታ እና አክሲዮን ድርሻ ሽያጭን በተመለከተ ፤ለግንቦት 30/2011 ዓ.ም ከጠዋቱ 4 እስከ 6 ሰዓት ለሚደረገው ጋዜጣዊ መግለጫ የአዳራሽ ኪራይ የተጠየቀ ሲሆን ፤
ሂልተን ሆቴል በደብዳቤ ለቀረበለት ጥያቄ ግንቦት 28 ቀን 2011 ዓ.ም አወንታዊ ምላሽ በደብዳቤ በመግለጽ፣ ክፍያ እንዲፈጸም በጠየቀው መሰረት በዚው ዕለት 12995 ብር (አስራ ሁለት ሺህ ዘጠኝ መቶ ዘጠና አምስት ብር ) ክፍያ ተፈጽሟል ።
ይሁን እንጂ በተገባው ህጋዊ ውል መሰረት፣ በዛሬው ዕለት ጥሪ የተደረገላቸው ጋዜጠኞች እና ጋዜጣዊ መግለጫ ለመስጠት የተገኙ የሰናይ መልቲ ሚዲያ መስራቾች ፣በቦታው ቢገኙም የተሳበው መግለጫ መስጠት አልተቻለም ።
ይህን ጉዳይ በተመለከተ የሆቴሉ የሽያጭ ክፍል እረዳት ስራ አስኪያጅ አቶ አንተነህ ሰርጸወልድ " ከሚመለከተው ክፍል ፍቃድ ካላመጡ መግለጫ እንዳይሰጡ" በማለት ከደህንነት ተደውሎ ስለተነገረን አሁን መግለጫ መስጠት አትችሉም ብሏል ። ለእኚህ ስራ አስኪያጅ የሰናይ መልቲ ሚዲያ መስራቾች "የሚመለከተው" አካል ማነው ?ይህን ማድረግ ከእኛ አይጠበቅም !ዝግጅታችን አጠናቀናል፣ ህጋዊ ውል ፈጽመናል ፣ መግለጫ እንድንሰጥ ወደ አዳራሹ እንድንገባ በሩ ይከፈትልን ፤ በማለት ጥያቄ ያቀረቡ ቢሆንም፤ አቶ አንተነህ የሆቴሉን ጥበቃዎችን በመጥራት የአዳራሹ በር በማዘጋት ፣" ይሄ ከእኔ አቅም በላይ ስለሆነ ፤ ጊቢውን ለቃችሁ ውጡልኝ " ብለዋል ።
የሰናይ መልቲ ሚዲያ መስራቾች ይህ'ን መንግስታዊ የሚዲያ አፈና ፣እዛው በመረጃና በማስረጃ በሆቴሉ ቅጥር ግቢ ለተገኙ የሚዲያ ተቋማት በመግለጽ ፣ ግቢውን ለቀው ወጥተዋል ።
ከላይ ለተዘረዘሩት የውል ስምምነት ማስረጃ ከዚህ ጽሁፍ ጋር ተያይዟል ፣እኔ'ም በቦታው ስለነበርኩ እማኝነቴን እገልፃለው።
ድል ለእውነተኛ ዴሞክራሲ !!!



Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes