H.Res 128 በኢትዮጵያ መንግስት ሎቢስቶች አማካኝነት ከድምፅ አሰጣጥ ስነስርአት እንዲዘገይ መደረጉ ታወቀ
ለኦክቶበር 2 , 2017 ሊደረግ የነበረው ኢትዮጵያን የሚመለከተው ህግ H.Res 128 መተላልፉን አስመልክቶ የኮንግረስ አባላት አዲስ ኢንፎርሜሽን ለኢትዮ አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል መኖሩን  ለኮሚቴው አስታውቀዋል።
ጉዳዩን በቅርበት የሚከታተሉት የኢትዮጵያውያን አሜሪካን ሲቪክ ካውንስል እና ኢትዮጵያን አድቮከሲ ኔትወርክ እንደገለፁልን ከሆነ የተላለፈበት ምክንያት ባለፈው ሳምንት ከአሜሪካን ባለስልጣናት የተነገራቸው የጊዜ ጥበት ሳይሆን፤ የኢትዮጵያ መንግስት በቀጠራቸው ሎቢስቶች አማካኝነት ከድምፅ አሰጣጥ ስነስርአት ለጊዜው እንዲወጣ ማስደረጋቸውን ለመረዳት መቻላቸውን አስታውቀዋል።
የውሳኔ ቀኑን መራዘም አስመልክቶ  አቶ አምሳሉ ካሳው በዋሽንግተን ዲስ ከሚተላለፈው የነፃነት ሬድዮ ድምፅ ጋር ባደረጉት ቃለ ምልልስ እንዳስታወቁት ይህ ህግ 128 ለጊዜው ለሌላ ጊዜ እንዲተላለፍ የሆነው በካሊፎርኒያው ተወካይ Kevin McCarthy። CALIFORNIA’S 23RD DISTRICT አማካኝነት መሆኑን ተናግረዋል።
http://hr128.org/h-res-128-%e1%89%a0%e1%8a%a2%e1%89%b5%e1%8b%ae%e1%8c%b5%e1%8b%ab-%e1%88%98%e1%8a%95%e1%8c%8d%e1%88%b5%e1%89%b5-%e1%88%8e%e1%89%a2%e1%88%b5%e1%89%b6%e1%89%bd-%e1%8a%a0%e1%88%9b%e1%8a%ab%e1%8a%9d/
 አያይዘውም እንደገለጹት ኢትዮጵያውያን በዚህ ተወካይ በአስቸኳይ በስልክና በደብዳቤ በመጠየቅ ይህ H.Res 128 ረቂቅ ህግ ለድምፀ ቀጠሮ ጊዜ እንዲያዝለት ግፊት ማድረግ ይኖርብናል ብለዋል።
የኢትዮጵያ ትግል እንዲህ በቀላሉ የሚያልቅ እንዳልሆነና ይህም ከብዙዎቹ የነፃነት ትግሎች በዲፕሎማሲው መስክ ጥቂቱ ነው ያሉት አቶ አምሳሉ፤ ይህ ሳያዘናጋን በዲፕሎማሲው ረገድ መቀዳጀት የሚኖርብንን ድል ልናረጋግጥ የምንችለው በሁሉም የኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ ተሳትፎ መሆኑን አስምረውበታል።
በተለይም በዚህ የካሊፎርኒያ ተወካይ አካባቢ የምንኖር ኢትዮጵያውያን በሚከተለው አድራሻ ተወካዩንና የቢሮ አማካሪዎቹን ማናገር ይጠበቅብናል።




Kevin McCarthy
CALIFORNIA’S 23RD DISTRICT
2421 Rayburn HOB
Washington, DC 20515
Phone 202-225-2915
Fax 202-225-2908
kevinmccarthy.house.gov
ዘመቻውም ተጠናክሮ መቀጠል ያለበትና እስካሁንም ድረስ በረካታ የአሜሪካ የምክርቤት አባላት 128 እየደገፉትና ከ70 በላይ አባላት ረቂቅ ሃሳቡን ስፖንሰር ማደረጋቸውንም አስታውቀዋል።
ይህ ለጊዜው ከድምፀ ውሳኔ ቀጠሮ የወጣ እና መቼ ለድምፅ እንደሚቀርብ ያልታወቀ እንጂ ሙሉ በሙሉ የወጣ አይደለም በማለት ተናገረዋል።
የኢትዮጵያ መንግስት ሎቢስቶችና ባለስልጣናት ኬቨን ማካርቲን በማናገር የአሜሪካ ህግ አውጪው ክፍል ይህን ህገ ረቂቅ የሚያሳልፉ ከሆነ ኢትዮጵያ በአስቸኳይ ማናቸውንም ትብብር ታቆማለች ሲሉ ለኬቨን ማካርቲ እንደተናገሩም ለማወቅ ተችሏል።
            ይህንንም አስመልክቶ የኮሎራዶው ተወካይ ኮንግረስማን ማይክ ኮፍመን ለኢትዮጵያውያን ባስተላለፉት መልእክት ላይ ይህ የምናደርገው በኢትዮጵያ የሰበአዊ መብት መከበር ጥያቄ ተጠናክሮ መቀጠልና በዚህ የሚቆም ትግል እንደሌለ እና ጉዳዩን እሰከመጨረሻው እንደሚገፉበት አረጋግጠዋል። አያይዘውም መንግስታቸው በአምባገነኑ የኢትዮጵያ መንግስት ላይ የሚያደርገውን የዲፕሎማሲ ጫና እንዲቀጥልና ዲሞክራሲያዊ ስርአት እንዲኖር ከኢትዮጵያውያን ጎን ሆነው ግፊቱን እንደሚያጠናክሩ ገልፀዋል።
        
ማይክ ኮፍመን ጨምረው ሲናግሩ እንዴት ሃገሬ አሜሪካ የራሱን ዜጋ በግፍ ለሚገል እና በየጊዜው የፖለቲካ መሪዎችን የሚያስርና የሚያንገላታን መንግስት ድጋፍ ልትሰጥ ትችላለች ስለዚህ ይህ እንዲሆን በምንም አይነት መንገድ መፍቀድ የለብንም የኢትዮጵያኖች ስቃይ ሊቆም ይገባል ብለዋል። አሁንም ይህ ረቂቅ ህግ እስኪሆን እንቀጥልበታለን። የኢትዮጵያ መንግስት አሁንም ዜጎቹን እየገደለ እያሰረ እና ከሃገር እያሰደደ ይገኛል ሲሉ አጠብቀው ተናግረዋል። ይህንንም የአሜሪካ መንግስት ታወግዛለች በማለት ንግግራቸውን አሰምተዋል።
ከH.Res 128 ረቂቅ ህግ ሌላ Sen. Res 168 በተጨማሪ ድምፅ ለማግኘት በወረፋ ላይ ይገኛል።

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes