የትግሬ እና የኦሮሞ ልሂቃን፣ ዐማራን በጅምላ ለመፍጀት የቀየሱት የተጠቂነት ፖለቲካ ሥልት

ለመሆኑ የተጠቂነት ፖለቲካ ሥልት ምን ማለት ነው? የተጠቂነት ፖለቲካ ሥልት፣ የአንድ ማኅበረሰብ ልሂቃን፣ ባልነበሩበት እና ባልኖሩበት የታሪክ ዘመን፣ በተለያዩ ፖለቲካዊ፣ ኢኮኖሚያዊም ሆነ ማኅበራዊ ጉዳዮች አስገዳጅነት የተፈጠሩ ግጭቶችን እና የተከሰቱ ክስተቶችን ለማብራራት የተጣመመ ትንታኔ በማቅረብ፣ ለራሣቸው የፖለቲካ ዓላማ ማሣኪያ አድርገው የሚጠቀሙበት ዘዴ ነው። እኒህ ልሂቃን በግጭቶቹ ወቅት ራሱም ጉዳት ደርሶበት፣ ነገር ግን የድል ባለቤት የሆነው አካል የወሰዳቸውን ዕርምጃዎች፣ ትክክለኞቹን ከሐሰት ፈጠራዎች ሣይለዩ፣ እንዲያውም ልብ ወለድ ድርሣኖችን በመጨማመር፣ «ይህ ተፈጸመብን፣ እንዲህ ተደረግን፣ ይህን ተቀማን፣ ይህ በደል ደረሰብን፣ እንዲህ ይሉናል፣ ወዘተርፈ» እያሉ ያልተባሉትን እንደተባለ በማራገብ፣ ያልተደረገውን እንደተደረገ በማቅረብ፣ «ተምኔታዊ ተጠቂነትን» እንደ ኃይል ማሰባሰቢያ ሥልት ይጠቀሙበታል። ይህ ዓይነቱ ዘዴ ለነገዳቸው አባሎች የሥነልቦና የበታችነትን፣ ተዋራጅነትን እና ተሸናፊነትን የሚያሸጋግር ከመሆኑም በላይ፣ ትውልዱ ትናንትን እንጂ ነገን እንዳያይ በመሸበብ፣ ለ«ተበደልኩ» ባዩም ሆነ «በዳይ» ለተባለው ወገን የወል መጠፋፊያ የሚሆን የበቀል ጎዳናን ይጠርጋል።
የዐማራው ነገድ በየዘመኑ በተለያዩ የውጪም ሆነ የአገር ውስጥ ኃይሎች ከፍተኛ የሆነ ግፍ እና በደል የተፈጸመበት መሆኑ ፀሐይ የሞቀው ሃቅ ነው። የዐማራው አባቶች ግን ምንጊዜም ቢሆን ለልጆቻቸው «የእነ እገሌ ነገድ/ጎሣ እንዲህ አደረጉን»፣ ወይም «እንዲህ ይሉናል» የሚል የሥነልቦና እና የሥነምግባር ስብራትን የሚፈጥሩ ትውፊቶችን ለልጆቻቸው አያስተላልፉም። በመሆኑም በተጠቃም ጊዜ ቢሆን ዐማራው በሥነልቦና እና ሥነምግባር ደረጃ በአጥቂዎቹ ላይ የበላይነቱን እንደያዘ እንዲቀጥል አድርጎታል። በዚህም የተነሣ በኢትዮጵያ ረጅም ታሪክ ውስጥ በተከሰቱ «የተገዛ አልገዝም፣ የገብር አልገብርም» ጦርነነቶች፣ ዐማራው በተለያዩ ነገዶች እና ጎሣዎች አያሌ ጥቃቶች እና በደሎች እንደደረሱበት ቢታወቅም፣ አንድም ጊዜ የተጠቂነት ፖለቲካን አራምዶ አያውቅም። የዐማራው ነገድ ታላቅነት የሚመነጨውም በአርቆ ተመልካቸነቱ ከዚህ «የተጠቂነት ፖለቲካ» ራሱን ያራቀ በመሆኑ ነው። በቆየው ትውፊት እንደሚነገረው፦ «ዐማራና ሠንበሌጥ አንድ ናቸው» ይባላል። ምክንያቱም ሠንበሌጥ ኃይለኛ ወዠቦ ዝናም ሲመጣ ለጥ ብሎ እንደሚያሳልፈው ሁሉ፣ ዐማራም ከዐቅሙ በላይ የሆነ ነገር ሲገጥመው አንገቱን ደፍቶ ያሣልፋል። እንዲሁም «የበቆሎ ሠብል እና ዐማራ መከራን ይቋቋማሉ። የበቆሎ ሠብል በቡቃያነቱ የሚያዝያን እና የግንቦትን ፀሐይ ጠውልጎ አሣልፎ፣ በክረምት ዝናም ለምልሞ፣ በጥቢ ወራት በመስከረም እና በጥቅምት እሸቱ እንደሚደርስ ሁሉ፣ ዐማራም የሚደርስበትን ማናቸውንም መከራ እና ስቃይ ተቋቁሞ በመጨረሻ የድል ባለቤት ይሆናል።» የሚሉት አባባሎች ዐማራ የዚህ የተጠቂነት ፖለቲካ ሰለባ አለመሆኑ ጉልህ ማሣያዎች ናቸው።
ዐማራው ለተጠቂነት ሥነልቦና ሰለባ ያልሆነባቸው ብዙ ምክንያቶች አሉ። ከባህላዊ ትውፊት እና ታሪካዊ መረጃዎች መገንዘብ እንደሚቻለው፣ ዐማራው ማግኘት እና ማጣትን፣ ማሸነፍ እና መሸነፍን፣ መግዛት እና መገዛትን ጠንቅቆ ያውቃል። ለዚህም የረዳው በዚች ዓለም ላይ ያሉ ሁሉም ነገሮች አላፊዎች እንደሆኑ፤ ቋሚዎቹ እና ፈራጆቹ ግን ታሪክ እና ሕዝብ ብቻ መሆናቸውን በኃይማኖታዊ ሥርዓቱ በሚገባ በመማሩ እንደሆነ ይታመናል። በመሆኑም «ዐማራ ገዛባቸው» በተባሉት ዘመናት እንኳን ልክ የዛሬው የትግሬ-ወያኔ ቡድን እንደሚያደርገው፣ በነገድ ፖለቲካ ላይ የተመሠረተ የኃብት ዘረፋ እና የሥልጣን ቅርምት አድርጎ አያውቅም። ዐማራው እንደ ትግሬ ልሂቃን የንብነት፣ እንዲሁም እንደ ኦሮሞ ልሂቃን የባሕር-ዛፍነት ባሕሪ የሌለው ስለሆነ፣ «ለብቻየ ልብላ እና ልጠቀም» ያለበት ወቅት የለም።
ንብ እና የትግሬ-ወያኔ አንድ ናቸው። ንብ ሩቅ አገር ተጉዛ፣ አበባ ቀስማ፣ ወደ ቀፎዋ ተመልሣ፣ ማር ትሠራለች። ሰው ንብ የሠራችውን ማር ለመቁረጥ ሲሞክር ተናድፋ ታባርረዋለች። የትግሬ-ወያኔም የኢትዮጵያውያንን ኃብት በሙሉ ከአገሪቱ አራቱ ማዕዘናት በመዝረፍ ወደ ትግራይ ያጓጉዛል። ትግራይ የገባ ንብረት ደግሞ የትግሬ ብቻ አንጡራ ኃብት ነው።
ዐማራው እንደ ኦነግ እና ኦሕዴድ የባሕርዛፍነት ጠባይ የለውም። በምድራችን ካሉት ራስ-ወዳድ ዕፅዋት መካከል ባሕርዛፍ አንዱ ነው። ባሕርዛፍ ከሥሩ እንኳን ሌላ ተክል፣ የራሱም ዘር ትንሽ ከዕድገቱ ጎተት ካለ አያሳድገውም፤ አቀጭጮ ያጠፋዋል እንጂ። ምንም እንኳን ኦነጎች የሻቢያ፣ ኦሕዴዶች ደግሞ የወያኔዎቹ ተላላኪዎች እና ትዕእዝ አስፈጻሚ ቢሆኑም፣ እንደ ባሕርዛፍ ከዘራቸው ውጪ ሌሎች ኢትዮጵያውያን በክልላቸው እንዲኖሩ አልፈቀዱም። «ኦሮሞያ ለኦሮሞዎች» በሚል የጭፍን ዘረኞች መፈክር በመመራት፣ ሌሎችን ኢትዮጵያውያን፣ በተለይም ዐማሮችን በጅምላ ጨፍጭፈዋል፣ አባርረዋል አሁንም ከዚህ ድርጊታቸው አልታቀቡም። ሆኖም እነርሱ «ኦሮሚያ» ብለው የሚጠሩት ግዛት፣ ከ፲፮ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አጋማሽ ጀምሮ በወረራ የያዙት መሬት ሲሆን፣ ጥንተ ሥረ-መሠረቱ ግን የዐማራው፣ የሐዲያው፣ የከንባታው፣ የዛዩ፣ የጠምባሮው፣ የአላባው፣ የሲዳማው፣ የጉራጌው፣ የአርጎባው፣ የሺናሻው፣ የጋሞው፣ የዳውሮው፣ የአንፊሎው፣ የየሙ፣ ወዘተረፈ ርስት የነበረ መሆኑ ይታወቃል። አልፎ ተርፎም እንደ ጋፋት፣ እናርያ፣ ዳሞት፣ ገንዝ፣ ወጅ፣ ቢዛሞ፣ አንጎት፣ ቤተ-ዐማራ እና የመሣሠሉትን ነገዶችን እና ታላላቅ የግዛት ስሞችን የኦሮሞ ወራሪዎች ሙሉ በሙሉ እንዳጠፏቸው ታሪካዊ ሃቅ ነው።
ዐማራው በማኅበራዊ ግንኙነቱም ሆነ በፖለቲካ አቋሙ እንደ ዋርካ፣ ዝግባ፣ ሾላ ዛፎች ነው። እኒህ ዛፎች በሥራቸው በርካታ የቁጥቋጦ እና ዕፅዋት ዘሮች እንዲበቅሉ፣ እንዲያድጉ እና እንዲራቡ ያደርጋሉ። ለምሣሌም ያህል ለአገራችን ለኢትዮጵያ ዋነኛ የውጭ ምንዛሪ ማግኛ የሆነው «አረንጓዴው ወርቅ» በመባል የሚታወቀው ቡና አድጎ፣ ለፍሬ የሚበቃው፣ በነዚህ ዛፎች ጥላ ሥር ነው።
ከዚህም በተጨማሪ አጋሙ፣ ቀጋው፣ እንኮዩ፣ ጠንበለሉ፣ ኮሽሙ፣ ሐረጉ ወዘተርፈ በእነዚህ ዛፎች መከታነት እና ጥላነት ሥር
ተንሠራፍተው ይራባሉ።
በአገራችን ታሪክ ዐማራው በዐማራነቱ ኢትዮጵያን ለብቻው ጠቅልሎ የገዛበት ወቅት ባይኖርም፣ በዐማራው ስም ኢትዮጵያ
ተገዛች በተባሉባቸው ዘመናት እንኳን፣ አንዳች ኃብትም ሆነ ንብረት ተዘርፎ አሁን ወያኔ «የዐማራው ክልል» ብሎ ወደከለለው አካባቢ
አልተጓጓዘም። የሌሎች ነገዶች እና ጎሣዎች አባሎችም «አገራችሁ አይደለምና ውጡ» የተባሉበት አጋጣሚ የለም። እንዲውም
በተቃራኒው ከታሪክ የምንገነዘበው፣ ዳግማዊ አፄ ምኒልክ፦ እንደ ንጉሥ አባ-ጅፋር አባ-ጎሞል፣ ራስ ጎበና ዳጨ፣ ፊታውራሪ
ኃብተጊዮርጊስ ዲነግዴ፣ ደጃዝማች ባልቻ ሣፎ፣ ደጃዝማች ገብረእግዚአብሔር (ኩምሣ) ሞረዳ፣ ደጃዝማች ጆቴ ቱሉ፣ ወዘተርፈ
የመሰሉት ስመጥር የኦሮሞ የጦር መሪዎችን ወደ ከፍተኛው የሥልጣን ማማ ያወጡ መሆናቸውን ነው። ይህ ሁሉ የዐማራው ሥነልቦና
የበላይነት ያለው እና የተጠቂነት ፖለቲካ ሰለባ ያለመሆኑ ውጤት ነው።
የተጠቂነት ስሜት የበታችነት ስሜት የሚወልደው አደገኛ እና ተወራራሽ የሥነልቡና በሽታ ነው። በዚህ ደዌ የተለከፉ
ልሂቃን፣ ለነገዳቸው አባሎች በዓለም ላይ ያለው መልካም ነገር ሁሉ ቢደረግላቸው እንኳን፣ ዘወትር ከማማረር እና ከማሤር
አይቆጠቡም። የበታችነት ስሜቱ ተላላፊ በሽታ የሚሆነውም፣ የነገዱ ልሂቃን የሆኑት የተጠቂነት ፖለቲካ አራማጆች፣ ነጋ ጠባ «እንዲህ
ሆንን፣ እንዲህ ተባልን፣ እንዲህ ተደረግን» በማለት ተከታዩ ትውልዱ ወደፊት ሣይሆን ወደኋሊት እንዲያይ በማድረግ፣ ለበቀል
እንዲነሣሣ ስለሚያደርጉት ነው። በዚህም ሁኔታ ተከታታይ ትውልዶች የበታችነት ስሜትን እንዲቀበሉ በመሣሪያነት በመጠቀም፣
የተጠቂነት ፖለቲካን ተሸካሚ የሆነ ማኅብረሰብን በመፍጠር፣ የዚያ ነገድ አባሎች ከዚህ ደዌ እንዳይፈወሱ ያደርጋሉ። ስለሆነም
የተጠቂነት ፖለቲካ ማራመድ፣ ቂም እና ጥላቻን አርግዞ በቀልን የሚወልድ የአመለካከት ስብራት ነው። ይህ ደዌ ደግሞ በቀላሉ
በሕክምና ሊፈወስ የማይችል ታላቅ ተላላፊ በሽታ በመሆኑ፣ አገራችን ኢትዮጵያ በዚህ ዓይነቱ የፖለቲካ አመለካከት አራማጆች
ስትታመስ ትኖራለች።
የተጠቂነት ፖለቲካ የሚያራምዱ ሰዎች ትናንትን እንጂ፣ ነገን አሻግረው ማዬት የሚችሉ አይደሉም። ወደ ኋላ እንጂ፤ ወደ
ፊት መመልከት የማይሹ ናቸው። በመሆኑም የእንቅስቃሴአቸው ዜማ በቀል ነው። በቀል ደግሞ ጥፋት ነው። ያለፈውን፣ እነርሱ በደል
ነው ያሉትን፣ በሌሎች ላይ ለመፈጸም መዘጋጀት ነው። ያውም ከጉዳዩ ጋር ተያያዥነት በሌላቸው ሰዎች ላይ! በደል በደልን
እንደሚወልድ ካለመገንዘባቸውም ሌላ፣በዳያችን ነው ያሉት አካል መልሶ ያኑ በደል ሊፈጽም የማይችልበት ምንም ዓይነት ማረጋገጫ
ሳይኖራቸውና ያ ዓይነት ጥቃት ተመልሶ በእነርሱ ላይ ሊፈጸም እንደማይችል የሚተማመኑበት ዘዴ ሳይኖራቸው፣ ለበቀል ከበሮ
ይመታሉ። በዚያም ቤት እሳት እንዳለ ይዘነጋሉ። የተጠቂነት ፖለቲካ ሰለባ መሆን በለቅሶ፣ በዋይታና ሰዎች በፈጠሩት የፈጠራ ድርሰት
ማመንን የግድ ስለሚል፣ባለቀሱና እንዲሆኖ ፤እንዲህ ተደርጎ ያላቸውን ሁሉ ዕውነት አድርገው በመቀበል ተከታይ ትውልዳቸው ያኑ
የተጠቂነት ፖለቲካን እንዲያራምድ ዉሸትንና ልብ ወለድ ድርሳኖችን በገፍ ያቀርባሉ። ይህም ትውልዱ መቻቻልን እና አብሮነትን
እንዲጠላ እንዲሁም መነጠልን ብቸኛ መንገድ አድርጎ እንዲነጉድ በማድረግ ከማኅበረሰብ ዕደገት ተፃራሪ በሆነ አቅጣጫ እንዲጓዝ
ያደርጉታል። ትርፉም ጥፋት፣ አመድ እና ፀፀት ይሆናል። ከኤርትራ መገንጠል የምንማረው ይህን ነው።
በኢትዮጵያ የፖለቲካ ታሪክ ውስጥ አያሌ የተጠቂነት ፖለቲካ አራማጅ የሆኑ ልሂቃን ነበሩ፣ አሉም። በእኒህ ልሂቃን ግፊት
የተነሣ የነገዳቸውን መጠሪያ ስም እስከማስቀየር መድረሳቸውን ስናስተውል፣ አሁንም ለትውልዳቸው በማስተላለፍ ላይ ያሉት
ትምህርት በተጠቂነት ፖለቲካ የተቃኘ መሆኑን አለመገንዘባቸውን ያመለክታል። ሆኖም ለሌላው ወገን እነርሱ በነባሩ ስማቸው ተጠሩ
ወይም «በዚህ ስም ጥሩን» ባሉት ተጠሩ፣ ነገሩ አቅማዳ ቀልቀሎ-ቀልቀሎ አቅማዳ ከመሆን ያለፈ ትርጉም አይኖረውም። የስም ለውጡ
ያስፈለገበት ዋናው ምክንያት «በዚያ ስም እንዲህ ተብለናል» ከሚለው ለመሸሽ በመሆኑ፣ ሽሽቱ የበለጠ ጥያቄን በማስነሣት፣ የጥንቱን
ማንነት በምርምር የበለጠ እንዲታወቅ ከማድረግ የዘለለ ጥቅም ያመጣል አይባልም። በመሆኑም የነገድ መጠሪያ ስም መቀየሩ
የበታችነት ስሜት መኖሩን ያረጋግጣል እንጂ፣ የበላይነትን ስሜት ያጎንጽፋል ተብሎ አይጠበቅም። በአጠቃላይ አነጋገር፣ የስም መጠሪያ
ለውጡ የማንንት ቀውስ የፈጠረው የተጠቂነት ፖለቲካ ውጤት ከመሆን አያልፍም።
ባለፈው ዓመት በ፪ሺህ፮ ዓ.ም. ማገባደጃ፣ አርሲ ውስጥ የኦሮሚያ ባህል ማዕከል ተብሎ በተገነባ ቅጥር ግቢ ውስጥ፣ «አኖሌ
ሠማዕታት» የተሰኘ ሐውልት ቆሟል። ሐውልቱን ያስገነባው የትግሬ-ወያኔ አገዛዝ ነው። ሐውልቱ ወደላይ በተዘረጋ የቀኝ እጅ መዳፍ
መሐል የተቆረጠ ጡት ጉች ያለበት ነው። ይህም ሐውልት እንዲወክል የተፈለገው፣ በዳግማዊ አፄ ምኒልክ የአገር ግንባታ ወቅት
በ«ገብር፥ አልገብርም» ሽኩቻ ምክንያት በተካሄደው ጦርነት፣ የዳግማዊ አፄ ምኒልክ ሠራዊት «በአርሲ ኦሮሞ ሴቶች ላይ አደረሰ»
የሚሉትን ጉዳት ለመዘከር እንደሆነ የሐውልቱ ባለቤቶች ገልጸዋል። አኖሌ፣ ተስፋዬ ገብረአብ «የቡርቃ ዝምታ» በሚል ርዕስ
ባሳተመው ልብወለድ መጽሐፍ ውስ ዋና ገጸ-ባሕርይ ነው። መጽሐፉን ያነበቡ ሰዎች፣ በዕውኑ ዓለም «ይህ ሰው ሌንጮ ለታ» ነው
የሚሉ አሉ። እርግጠኛው የአኖሌ ገጸ-ባሕርይ ማንን እንደሚወክል የሚያውቁት የልብወለድ ታሪኩ ጠንሣሾች የሆኑት የወያኔ እና
የሻዕቢያ ሰዎች ብቻ ናቸው። ይህ ልብወለድ መጽሐፍ ዐማራን እና ኦሮሞን እስከ ወዲያኛው እንዳይገኛኑ በማድረግ፣ ኢትዮጵያን እና
ኢትዮጵያዊነትን ለማጥፋት ታጥቀው በተነሱት በሻዕቢያ እና በወያኔ የተቀነባበረ እንደሆነ ያነበቡት ሁሉ የሚስማሙበት ጉዳይ ነው።
ነገሩ ያልገባቸው እና የተጠቂነት ፖለቲካ አራማጅ የሆኑት የኦነግ እና የኦሕዴድ ጀሌዎችም «ለካ ይኸን ያህል ተበድለን ኖሯል» በሚል
ስሜት፣ ልብወለዱን ገሃድ፣ ውሸቱን ዕውነት በማድረግ፣ የተሸናፊነት እና የተጠቂነትን ሥነልቦና በአሁኑ የኦሮሞ ትውልድ ላይ ለመጫን
ቋሚ የመልዕክት ማስተላለፊያ ሐውልት ሠርተው ስናይ፣ የዘመናችን የኦሮሞ ልሂቃንን የቱን ያህል ለተጠቂነትና ለተሸናፊነት ሥነልቦና
እንደተጋለጡ እናያለን።
በትክክለኛው አቅጣጫ ከታዬ፦ በሐውልቱ ሊተላለፍ የተፈለገው መልዕክት የሚወክለው የዐማራውን የጦርነት ባህል
ሣይሆን የኦሮሞ ወራሪዎችን ታሪካዊ ድርጊቶች ነው። ዛሬ ሳይቀር ብልት መስለብና ጡት መቁረጥ ተዘውትሮ የሚታየው በኦሮሞው
ማኅበረሰብ እንጂ፣ በየዐማራው አለመሆኑን ትውልዱ በየዕለቱ የኑሮ ገጠመኙ የሚያየው ስለሆነ፣ ማንም ቢሆን እንዲህ ያላው ሥራ
የራሱ የኦሮሞ እንጂ፣ የዐማራው ነው ብሎ ይቀበለዋል ለማለት አይቻልም። ጡት የመቁረጥ እና ብልት የመስለብ የወራሪነት ባህል፣
በዐማራው የታሪክ እና የባህል ትውፊት መኖራቸውን የሚያሳዩ መረጃዎች ሊያቀርብ የሚችል ሰው ፈጽሞ የለም። ትናንት «ጋላ» ይባል የነበረው፣ ዛሬ ኦሮሞ በመባሉ ብቻ «የዚህ ባህል ባለቤት አይደለም» ካልተባለ በስተቀር፣ ሰለባ እና ጡት መቁረጥ ያለአንዳች ጥርጥር የኦሮሞ ባህል ነው። አንድ የኦሮሞ ወጣት የወደዳትን ሴት ለማግባት፣ ሰለባ መጣል ግዴታው እንደነበር ይታወቃል። ዛሬም ድረስ ይህ ድርጊት በኦሮሞ ማኅበረሰብ ተወላጆች አማካይነት ከእነርሱ ነገድ ወጪ በሆኑ ወንዶች ላይ ይፈጸማል። ይህን የሚያውቁ፣ በተግባርም ያከናውኑ የኦሮሞ ሰዎች ባሉበት እና ሰለባ ከኦሮሞ ባህል ውስጥ ዓይነተኛው መሆኑ በግልጽ በሚታወቅበት ሁኔታ፣ « የእምዬን እከክ በአብዬ ልክክ» እንዲሉ፣ ሰለባን እና ጡት ቆረጣን ወደ ዐማራ ማዞር፣ ራስን ካለማወቅና ራስን ሆኖ ካለመገኘት ሌላ የትውልዱን የማመዛዘን ችሎታ ዝቅ አድርጎ መመልከት ከመሆን ውጭ ሌላ ትርፍ ያመጣል ተብሎ አይጠበቅም። ትርፍ ያመጣል ከተባለም ትውልዱን ለበቀል ማነሳሳት እና የመጠፋፋትን ከበሮ መደለቅ ይሆናል። ይህ ደግሞ ለወንጃዮቹም ለኦሮሞ ልሂቃን አይበጃቸውም። ለሁሉም የሚበጀው፣ ወደኋላ ማየትን ትቶ ወደፊት በመመልከት፣ የጋራ ቤታችን የሆነችውን ኢትዮጵያን እንዴት እንገንባ? በኢትዮጵያውያን መካከል መቻቻልን እና በሰላማዊ ሁኔታ አብሮ መኖርን እንዴት እናስፍን? በሚሉት ዙሪያ መመካከሩ ነው። ይህ ካልሆነ ግን ዐማራውም የሚያነሣቸው እጅግ መሠረታዊ ጉዳዮች ይኖሩታል።
በነባራዊ ዓለም የሌለ እና ያልነበረ፣ የተስፋዬ ገብረአብ የልብወለድ ድርሰት ውጤት የሆነው የአኖሌ ሐውልት የቆመበት ቦታ እኮ፣ እስከ ፲፮ኛው መቶ ክፍለዘመን አጋማሽ ድረስ የሐዲያዎች እና የከንባታዎች መኖሪያ የነበረ ነው። ዛሬ ኦሮሞው ከደቡብ እስከ ሰሜን፣ ከምዕራብ እስከ ምሥራቅ ተንሰራፍቶ የሚገኝበትን ቦታ የያዘው በወረራ ነው። ኦሮሞው ሲወርር ደግሞ የወረረውን ሕዝብ በጅምላ እየገደለ፣ የማረካቸውን ወንዶች ብልት እየሰለበ የሴቶችን ጡት እየቆረጠ እንደሆነ በታሪክ የተረጋገጠ ሃቅ ነው። ዛሬ የኦሮሞው ቁጥር ከሌሎች የኢትዮጵያ ነገዶች በአንፃራዊ ሁኔታ በልጦ የመገኘቱ ሚስጢርም ሌላ ምንም ሳይሆን፣ ከ፲፮ኛው መቶ ክፍለ-ዘመን አጋማሽ ጀምሮ ባደረጉት የመስፋፋት ወረራ ወቅት፣ ከግራኝ አህመድ ጭፍጨፋ የተረፈውን ኢትዮጵያዊ እነርሱም በተራቸው በጅምላ በመፍጀታቸው እና በመስለባቸው የተነሣ ነው። ይህ ታሪካዊ ሃቅ ነው። ሆኖም ነገሩ «ብጥለው ገለበጠኝ» ነውና፣ በኦሮሞው ወረራ የተጎዳው ሌላው ኢትዮጵያዊ ሆኖ ሳለ፣ የተጠቂነት ሥነልቦና ስለሌለው ብቻ «ይህ ግፍ በኦሮሞዎች ተፈጸመብን» ባለማለቱ፣ ጉዳት አድራጊዎቹ ኦሮሞዎች እንደ ተበዳይ ሐውልት መሥራታቸው እጅግ የሚያስገርም ነው።
መቼም የአኖሌን መታሠቢያ ሐውልት በማቆም የኦሮሞ ሕዝብ የሚጠቀመው አንዳችም ቁሣዊ ጥቅም አለ አይባልም። ስለሆነም በዚህ የልብወለድ የፈጠራ ሥራ ተመርኩዞ በቆመው ሐውልት የሚጠቀሙት የኢትዮጵያ ጠላቶች ብቻ ናቸው። ምክንያቱም የኢትዮጵያውያንን አንድነት ንደውበታል። በድርጊታቸውም ኢትዮጵያ ውስጥ ከፍተኛ የሕዝብ ቁጥር ያላቸውን የዐማራን እና የኦሮሞን ነገዶች እንዳይገናኙ የሚያደርግ ጥልቅ ጉድጓድ ቆፍረዋል። ሁለቱንም ለዝንተ-ዓለም በአጥፊና በጠፊነት እንዲቆሙ አድርገዋል። እንዲህ ያለው የዐማራ-ኦሮሞ መናቆር፣ ከአናሣው የትግሬ ነገድ የበቀሉት የትግሬ-ወያኔዎች የኢትዮጵያን ሕዝብ ላለፉት ፳፫ ዓመታት ቀጥቅጠው እንዲገዙ የተመቻቸ ዕድል እንደሰጣቸው ሁሉ፣ ለወደፊትም ላልተወሰኑ ዓመታት አገዛዙ እንዲቀጥል በሩን ወለል አድርጎ ይከፍትላቸዋል። ሆኖም ሠሞኑን በተለያዩ የሕዝብ መገናኛ ዘዴዎች እንደተገለፀው፣ በአሶሳ፣ በበደኖ፣ በአሰቦት ገዳም፣ በወተር፣ በአርባጉጉ እና በሌሎችም ሥፍራዎች ይኖሩ በነበሩ የዐማራ ተወላጆች ላይ የጅምላ ጭፍጨፋ ዋና አስፈፃሚ የነበረው ሌንጮ ለታ እና ጓደኞቹ ወደ ኢትዮጵያ ሊገቡ (የገቡ) መሆኑ ይሠማል። ሌንጮ ለታ እና ሌሎችም የኦነግ አመራር ጓደኞቹ፣ ትላንትም ሆነ ዛሬ የሻቢያ እና የወያኔ ዓላማ አስፈፃሚዎች መሆናቸውን አገር ያወቀው፣ ፀሐይ የሞቀው ጉዳይ ነው። ስለዚህ የእነ ሌንጮ ዳግም ወደ ወያኔ መጠጋት ተልዕኮ ሌላ ሣይሆን ቀደም ብለው የጀመሩትን አስፀያፊ የዐማራ የጅምላ ጭፍጨፋቸውን ለመቀጠል እንደሆነ ማንም ኅሊና ያለው ሰው ይገነዘበዋል። እኒህ ሁሉ ድርጊቶች የሚከናወኑት፣ የዐማራውን ነገድ ሆን ብሎ ከምድረ-ገፅ ለማጥፋት ስለሆነ ዐማራው ከያዘው የቀን ሠመመን ሊነቃ ይገባል። ዐማራው የሥነልቦና የበላይነቱን ጠብቆ፣ እንደትግሬ እና ኦሮሞ ልሂቃን «የተጠቃን» ሥነልቦና ሰለባ ሣይሆን፣ ሊያጠፉት የተሰለፉትን «አውቀንባችኋል» ማለት እንዲችል የአኖሌ ሐውልት ጥሪ እያቀረበለት መሆኑን አስተውሎ፣ ከወዲሁ ሁለንተናዊ ዝግጅት ሊያደርግ ይገባዋል። በዚህ ረገድ የዐማራው ምሁራን ፊታውራሪዎች ሆነው፣ የአሁኑን እና ተከታዩን የዐማራ ትውልድ ከፈጽሞ ጥፋት የመታደግ ግዴታ አለባቸው። ምንጊዜም ቢሆን የአኖሌ ሐውልት የተገነባው ዐማራውን ለማጥፋት ለተጀመረው አዲስ ዙር የጅምላ ጭፍጨፋ ዘመቻ የጥሪ ደወል መሆኑን ዐማራው ሊጠራጠር አይገባም።
ዐማራን ከፈፅሞ ጥፋት እንታደግ!
ፈለገ-አሥራት የትውልዳችን ቃልኪዳን ነው!
ኢትዮጵያ ለዘለዓለም ትኑር!http://ethiopianvoices.wordpress.com/2014/01/23/%E1%8B%A8%E1%89%B5%E1%8C%8D%E1%88%AC-%E1%8A%A5%E1%8A%93-%E1%8B%A8%E1%8A%A6%E1%88%AE%E1%88%9E-%E1%88%8D%E1%88%82%E1%89%83%E1%8A%95%E1%8D%A3-%E1%8B%90%E1%88%9B%E1%88%AB%E1%8A%95-%E1%89%A0%E1%8C%85/

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes