በሶስተኛው ይሁዳ ጣላችሁ

   በሶስተኛው ይሁዳ ጣላችሁ
ክቡራት እና ክቡራን የዚህ ፅሁፍ ተከታታዮቼ በያላችሁበት ሰላምታዬ ይድረሳችሁ እያልኩ መቼም የሐገር ነገር ሆድ ይፍጀው ተብሎ ዝም የሚባል ባለመሆኑ እየሆነ ስላለው እና ስለተሰማኝ ስሜት ትንሽ ልል ወደድኩ
ሐገር ማለት እናት ናት!!! ሐገር ማለት ሁሉሉ ….ነገር ናት !
 የሐገርን ሉአላዊነት ማስከበር ደግሞ ከሰንደቅ ዓላማዋ ይጀምራል፤
ለዚያም ነው ጣልያኖች 1928 መላው ኢትዮጵያን ወረው ከአስመራ ለትርጉም ወሰደውት የነበረው ጀግናው ዘርዓይ ደረስ ከእለታት ባንዱ ዓመታዊ በአላቸው ላይ የሃገሩን የአርበኝነት ዩኒፎርም እስከነ ሙሉ ትጥቁ ጎራዴውን ጨምሮ ለብሶ በዓሉ ቦታ እንዲገኝ ካረጉት በሁዋላ የእምዬ ኢትዮጵያን ሰንደቅ ዓላማ መሬት ላይ አንጥፈው እየተፉ ሲያልፉ ጎራዴውን መዞ አጠገቡ ካሉት ወታደሮች በመጀመር የጣልያን ሹማምንቶችን አንገት እየቀነጠሰ  በመጣል ታላቅ ገድል የሰራው.
አዎ!!! በከፍተኛ የሐገር ፍቅር ስሜት እንደነበልባል እሳት ውስጡ እየተንቀለቀለ በታላቅ ቁጣና እልክ የመዘዘውን ጎራዴ ከሀፎቱ ማስመለስ የሚችል አንዳችም የሰው ሀይል እንደሌለ የተረዱት ጣልያኖች በጥይት እግሩን መተው እስኪጥሉት ድረስ አርበኛችን ዘርአይ ደረስ ብቻውን ይህንን ገድል ፈፅሙዋል!!!
ታዲያ ምነው እናንተ?
ለዛሬው ፅሁፌ እና ለዚህ ጥያቄዬ መነሻ የሆነችኝ ከወደ ጀርመን አካባቢ ስትንከባለል ያየሁዋት ፅሁፍ ስትሆን እንዲህ በማለት ትጀምራለች :-
ውድ የመማክርት ጉባኤ አባላት በዶ/ አቢይ አሕመድ የፍራንክፈርት ጉብኝቱ ወቅት በተፈጠሩ ችግሮች ዙሪያ ያቀረብናቸው ቀጥተኛ ጥያቄዎች በቆንስላ /ቤት ሀላፊዎች በኩል መልስ ባያገኙም ዘግይተውም ቢሆን ለተፈጠሩት አጠቃላይ ችግሮች እውቅና ሰጥተው ሕዝቡን  ይቅርታ ጠይቀዋል ትልና  ፍራንክፈርት ያለው የኢትዮጵያ ቆንስላ /ቤት በአካባቢያችን ለሚገኙ ሕዝባዊ አደረጃጀቶች ተወካዮች 14/12/2018 የስብሰባ ጥሪ አደርጓል። ምንም እንኳን በእኛ በኩል ብዙ ግልፅ ያልሆኑና ያልተመለሱ ጥያቄዎች ቢኖሩም  ስብሰባውን መሳተፍ እንደሚገባን ተስማምተናልእያለች ትቀጥላለች።
 በጣም የሚገርመው ደግሞ ይህ የመማክርት ጉባኤ ይህንን መላው ኢትዮጵያውያንን ያስቆጣ የፍራንክፈርቱን ዝግጅት አስመልክቶ በኑቨምበር 24/2018 ያወጣውን ጠንካራ የአቁዋም መግለጫ ይሰጡ የነበሩት ጭምርም አሁን አስተላለፍን ባሉት ውሳኔ ተሳታፊ መሆናቸው ነው። 
 ስለዚህ ለምን? የሚለውን ጥያቄ ልጠይቃቸው ወደድኩ ግን ለምን?
ጀንበር ሳትጠልቅ አስር ጊዜ እየተገለባበጣችሁ፤የምትይዙ የምትጨብጡትን አጥታችሁ፤ምንም ይሁን ምን አጋጣሚውን ተጠቅማችሁ ትንሽ ነገር ለማግኘት ስትሮጡ ሕዝብ ዘንድ ያለው ሀቅ እያነቃችሁ በሌላ ጊዜ ደግሞ የግል ኢጎዋችሁ እያሸነፋችሁ ምንም ይሁን ምን አጋጣሚውን ተጠቅማችሁ ትንሽ ነገር ለማግኘት ስትሮጡ ከግል ፍላጎታችሁ እና ከህሊናችሁ ጋር ከወዲህ ወዲያ እየተላተማችሁ ሰንደቅ ዓላማችንን ባደባባይ አዋርዶ ወደቅርጫት ካስወረወረ ከጀርመን በርሊን ኢምባሲ እና ከፍራንክፈርቱ ኮንስላ ጋር የምትሞዳሞዱት በሙሉ:- ሕዝቡን የእናንተ የሐሰት ፕሮፓጋንዳ ሰለባ እያደረጋችሁ ስታችሁ አታስቱት!
ከቻላችሁ ህሊና ይበልጣል እና ከህሊናችሁ ጋር ታርቃችሁ እንደ ድሩዋችሁ ለሕዝብ እና ለሐገር ደህንነት!፤ለሰንደቅ ዓላማችን ክብር በጋራ እንጩህ፤ዛሬም እንደትላንቱ ከአንድነት ይልቅ መለያየት ተፈጥሮ እነሱ እና እኛ የሚል ልዩነት እንዲፈጠር ያደረጉትን በጋራ እንታገላቸው!!!

   (የኢትዮጵያን ጠቅላይ ሚንስትር ዶክተር ዓብይን ለማግኘት ከመላው አውሮፓ የተሰባሰበውን ኢትዮጵያዊ የያዘዉን የኢትዮዽያ ሰንደቅ ዓላማ በር ላይ ወደቅርጫት እያስወረወሩ የፅንፈኞቹን በገፍ አስገብተው ኢትዮጵያዊነትን ሊያዋርዱ የሞከሩበት መድረክ)

ይህንን ማድረግ ካልቻላችሁ ግን እራሳችሁን ችላችሁ ከእነሱ ጋር ተጠቃለሉ እንጅ በቆንስላ ቢሮው የተፈፀመውን ሸፍጥ እያወቀ የሚከተላችሁ ስለሌለ የሌላውን ዓላማ ለማሳት የምታደርጉትን ቅስቀሳ አቁሙ።
27ዓመት የጭንቅ ዘመንን አብረን ስንታገል የነበራችሁ በጀርመን የምትኖሩ ሐገር ወዳድ ጉዋዶቻችን:- አስተባባሪ ሆነን ገባን ባላችሁበት ዝግጅት እንዴት ይህ ሁሉ አሻጥር ተሰርቶ ባደባባይ ሊያዋርዱን ቻሉ?!
ድሮ 27ዓመቱን የጭንቀት ዘመናችንን ሲያራዝሙ የነበሩት ካሮጌው ዘመን ካድሬዎች ጋር ሆነው ድንጋይ ሲያቀብሉ የነበሩት ናቸው! ታዲያ እናንተም ዛሬ ያመናችሁን ሕዝብ ከድታችሁ ከእነሱ ጋር ምነው ልታይ ልታይ አበዛችሁ እያልን በእልክ ፣በቁጭት እና በንዴት የሚወርደው እምባችንን እያፈሰስን የቁጣ በትር ስናወርድባችሁ የነበረው የእኛ ስላልናችሁ ነበር።
 በወቅቱ ይህንን የቁጣ በትር ሲያወርዱባችሁ ከነበሩት ውስጥ ደግሞ አንዱዋ እኔ ብሆንም በሁዋላ ግን ኢትዩጵያዊነትን አዋርዶ ሰንደቅ ዓላማችንን ቅርጫት ውስጥ ያስወረወረው የፍራንክፈርቱ የኮንስላ ቢሮ ዝግጅቱ በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተዋፆ ላደረጋችሁ ኮሚቴዎች ልማታዊ የምስክር ወረቀት እና የእራት ግብዣ አዘጋጅቻለሁ ተጋበዙልኝ ብሎ ያስተላለፈውን ጥሪ አብዣኞቻችሁ ቦይኮት አርጋችሁ በሰጣችሁት ጠንካራ መግለጫ በጣም መደሰት ብቻ ሳይሆን መግለጫውን የሰጣችሁትን ስሜት ሁሉ አነብ ስለነበር :-በመግለጫችሁ ያስተላለፋችሁ መልእክት የሁላችንንም ስሜት ያንፀባረቀ በመሆኑ በደስታ መፈንደቄን ልሸሽጋችሁ አልፈልግም!፤በተለይ አቶ ወንደሰን መግለጫውን የሰጠበት ስሜት ዎው የሚያስብል ነው!!!፤ብራቮ ይሄ ነው ለዓላማ ፅንቶ መቆም ብዬ አደነቅኩ።
አቶ ሥዩም ሀብተማሪያምአቶ ምህረተአብ ሙሉጌታ የኢትዮጵያ ኤምባሲ ጀነራል ኮንሱል በፍራንክፈርት ግልፅ ደብዳቤበሚል በግላቸው እንደገና የፃፉትን ሳይማ ማንይቻለኝ የኢትዮጵያ ልጆች አሁንም አሉ ብዬ በድጋሚ ፈነደቅኩኝ
ይህ እኔም ሆንኩ ሕዝቡ የተደሰተበት መግለጫችሁ ሶስት ሳምንት ሳይሞላው እና ቀለሙም ሳይደርቅ ዳግም ስትሙለጨለጩ በማግኘቴ ግን በእጅጉ አዘንኩ!እና በየግል ኢሜላችሁ የላከውን ጥሪም ተቀብላችሁ አንዳንዶቻችሁ ለመሄድ መወሰናችሁን እና ይባስ ብሎም አንዳንድ ቅስቀሳዎችን የምታደርጉባቸውን ፅሁፎች ሳይ የፍራንክፈርቱ ይሁዳም በሶስተኛው ጠልፎ እንደጣላችሁ ተረዳሁ።
ይኸውም :- (በ፩ኛው ሙከራው ):-የይስሙላ አስተባባሪ አድርጎ የተጠቀመባችሁ እና እጁ ሊያስገባችሁ የጣረው የፍራንክፈርቱ ይሁዳ ውስጥ ለውስጥ በሰራው አሻጥር ኢትዮጵያዊነት ባደባባይ ሲዋረድ ሕዝቡ ተቆጥቶ የቁጣ በትሩን በእናንተም ላይ እያወረደ አይናችሁ ላፈር ሲላችሁ እንዴት እንዲህ ይሆናል እኛስ በማናቀው ነገር እንዴት አብረን እንሰደባለን ብላችሁ ሸሻችሁት።
 (2ኛው:- ሙከራው):-  ሰንደቅ ዓላማችንን አዋርዶ ቅርጫት ያስወረወረበትን እና እስከዛሬ መላው ኢትዮጵያዊ በእልክ እና በቁጭት ውስጥ ያለበትን  የፍራንክፈርት ዝግጅት በስኬት እንዲጠናቀቅ አስተባባሪ ኮሞቴ ሆናችሁ ላገዛችሁኝ ግብዣ እና የምስክር ወረቀት አዘጋጅቻለሁ የሚል ጥሪ አቅርቦ በመጋበዝ ዛሬም እንደትላንቱ ውስጥ ለውስጥ እያደራጀ ለሚፈፅማቸው እኩይ ተግባሮቹ  እጁ ሊያስገባችሁ ያደረገው ሙከራ የውስኪ ስጦታ ጭምር ከታደሉት ጥቂት አለቅላቂዎች ከመሄዳቸው በቀር ይህም ሳይሳካለት ቀረ።
 (3ኛው ሙከራው ):- ግን ከግብዛው እና ከልማታዊ ምስክር ወረቀቱ በተጨማሪ ውስኪም ተቀብለው የወጡት እንዴት አድርገው እናንተንም እንዳጠመዱዋችሁ ባናውቅም የፍራንክፈርቱ ይሁዳ በየግል -ሜላችሁ ያደረገውን ጥሪ መቀበላችሁ ግን የይሁዳው ሶስተኛ ሙከራ ጠልፎ እንደጣላችሁ አውቀናል።
ለዚያም ነው እውነታውን ልባችሁ እያወቀ አንዴ ሄደን የሚሉትን እንስማ ምናምን የሚል አስር ምክንያት እየፈጠራችሁ ሕዝቡን እናንተም ለማደናገር የምትሞክሩት!
 ምንም ብታደርጉ ግንሊበሉ ያሰቡዋትን አሞራ ስምዋን ይሉዋታል ጅግራ” ካልሆነ ትላንት እናንተ አስተባባሪ ሆነን ገባን ያላችሁት ዝግጅት አስተባባሪ የሆኑት የጀርመን በርሊን ኢምባሲ እና የፍራንክፈርቱ ኮንስላ የአሮጌው ዘመን ቅሪቶች :-ታሪክ ይቅር የማይለው፤በየትኛውም ወቅት እና ጊዜ ለፍርድ አቅርበን ልንሞግታቸው የምንችልበት እንዴትም ብትሉ ሊሸፈን የማይችል ትልቅ ወንጀል ፈፅመውብናል።
   ይህቺን ሰንደቅ ዓላማ እና ኢትዮጵያዊ ማንነቴን ባደባባይ ያዋረደ ማንኛውም ሰው ለኔም ከወንጀለኛም በላይ ወንጀለኛ ስለሆነ ማርያምን ምሬም አልምረው።
ከላይ እንዳሰፈርኩት ደግሞ ሁላችንም የምንስማማበት የሐገርን ሉአላዊነትን ማስከበር ማለት ከሰንደቅ ዓላማ ይጀምራል!
አያት ቅድማያቶቻችን፣እናት አባቶቻችን፣እህት ወንድምቻችን የተሰውበት፤ትውልድ ተገብሮ የኢትዮጵያዊው ብቻ ሳትሆን የመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት አርማ የሆነችው ሰንደቅ ዓላማችንን ባደባባይ ለማዋረድ ባደረጉት እኩይ ተግባር የቱን ያህል ልባችን እንዳዘነ ፤እልክ እና ቁጭት ውስጥ እንደ ገባ የሚገባ ይገባዋል።
ሐገር ማለት  እናት፣አባት፣እህት፣ወንድም፣ሚስት፣ባል ፣ልጅ፣ብቻ ሐገር ሁሉንም ናት! ፤ሁሉም ነገር ሁሉም ነገር የሚያምረው ሐገር ሲኖር ብቻ ነው!
ታዲያ  እናንተ እንደምትሉት ልባችን በእጅጉ ያዘነበት እና ኢትዮጵያዊነታችን ባደባባይ የተዋረደበት የዚህ ዝግጅት አስተባባሪው አቶ ምህረተ አብ የጥያቄያችን 1/4ኛን መልስ እንኩዋን ባግባቡ ያልመለሱበት ይልቁንም ለሰሩብን ሸፍጥ እና ሴራ ሰው አዘጋጅተው እኔ ነኝ እንዲል አድርገው እራሳቸውን ከደሙ ንፁህ ለማድረግ ያደረጉት ሙከራ የትላንትናውን የፋሺስት ወያኔ እኩይ ተግባር ያስታወሰን እና ዛሬም ኢትዮጵያችንን ለማፍረስ የሚሮጡ የአሮጌው ዘመን ቅሪቶች በየመንግስት መዋቅሩ ውስጥ ተሰግስገው ብዙ ህይወት የተገበረለትን የለውጥ ጭላንጭል ለመቀልበስ በትጋት እየሰሩ መሆናቸውን በደንብ እንድንረዳ ማድረግ ብቻ ሳይሆን ዛሬም እንደትላንቱ ኢትዮጵያዊ ማንነታችንን ለማንቁዋሸሽ እና ለማዋረድ የሚሞክሩትን እነዚህ ከዘመኑ ጋር መዘመን ያልቻሉትን የኢምባሲ እና ኮንስላ ቢሮዎች ፀድተው ኢትዮጵያዊ መልክ እስኪይዙ ድረስ አጥብቀን መታገል እንዳለብን እና ይልቁንም ውስጥ ለውስጥ በሚዘረጉት መዋቅራቸው ለሌላ 27 ዓመት ባርነት እንዳይዳርጉን ለውጡን ተግተን መጠበቅ እንዳለብን እና ልንታገላቸው እንደሚገባ በደንብ የተረዳንበት ሁኔታ ነው ያለው።
ታዲያ ኢትዮጵያዊ ማንነታችንን እያንቁዋሸሹ እና እያዋረዱ ሌላ ማንነት ሊጭኑብን የሚሞክሩት የአሮጌው ዘመን ቅሪቶች ለፈፀሙብን እኩይ ተግባር ፍርድ ቤት አቅርበን ልንሞግታቸው ሲገባ አይ ዘግይተውም ቢሆን በተወሰነ መልኩ ይቅርታ ጠይቀዋል ምናምን ማለት ምን ማለት ነው? የትኛውንስ ይቅርታ ነው የጠየቁት? አስበው እና አቅደው የመላው ኢትዮጵያዊውን ልብ አሳዝነው እልክ እና ቁጭት ውስጥ እንድንገባ እና ዛሬም ከአንድነት ይልቅ መለያየትን አንፀባርቀው እነሱ እና እኛ ብለን እራሳችንን ወደሁዋላ እንድንስብ ያደረጉበት ዝግጅት በስኬት ተጠናቁዋል ብለው ውስኪ እና ልማታዊ ምስክር ወረቀት ያደሉበት ዝግጅት???
 ብቻ በሁዋላ እማዬ ምነው በእንቁላሉ በቀጣሽኝ እንዳይሆንብን ሁሉንም ነገር እያተስተዋልን ቢሆን ጥሩ ነው። ደሞ ምነው ትላንት እናንተም የዚህ እኩይ ተግባር ተባባሪ ተደርጋችሁ  መላው ኢትዮጵያዊ በእልክ እና በቁጭት ያንን ሁሉ የቁጣ በትር ሲያወድባችሁ እንዳልነበር በሁዋላ በእጅጉ የተደሰተበት መግለጫችሁ ቀለሙ ሳይደርቅ አብራችሁ መሞዳሞድ አማራችሁ?
ስለምን ከእናትም በላይ እናት የሆነችውን እና እንኩዋን እኛ የመላው ጥቁር ሕዝብ ኩራት የሆነችው ኢትዮጵያችንን ባደባባይ እያንቁዋሸሹ ሰንደቅ ዓላማዋን ያዋረዱብንን እና ሁላችንንም እልክ ፣ቁጭት እና ንዴት  ውስጥ የከተቱንን የፍራንክፈርት ኮንስላ ሰራተኞች እና ግብረአበሮቻቸውን ወንጀል ልናቀልላቸው እንሞክራለን?
እባካችሁ ያስነኩዋችሁ ማኖ ካለ እዚያው እዳችሁን ቻሉ እንጅ በሶስተኛ ሙከራቸው ጠልፈው ወደጣሉዋችሁ ይሁዳዎች የሚለው ጉትጎታችሁን አቁሙ !!!
ከየሺሐረግ በቀለ

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes