የሬሚታንስ /ሃዋላ/ ተአቅቦ የማህበራዊ ሚድያ ዘመቻ ጥሪ
የዘመቻ ጊዜ፦ ከዛሬ ጃንዋሪ 01 2018 እስከ ማርች 31 2018 ድረስ ለሦስት ተከታታይ ወራት
ለዘመቻው የሚውሉ ሀሽታጎች:-
#Ethiopia : የዘመቻው ዓላማ፦ ሁሉም ኢትዮጵያዊ እንደሚገነዘበው፣ በዚህ ወቅት ህዝባችን ነጻነቱን ለማግኘት እና የሀገሩ ባለቤት ለመሆን ከፍተኛ መስዋእትነት እየከፈለ ይገኛል። ከሁለት አመት በላይ የዘለቀው ህዝባዊ እምቢተኝነት ህዝቡን ውድ ዋጋ ቢያስከፍለውም የህወሓትን መንግስት ከፍተኛ ቀውስ ውስጥ አስገብቶታል። ከላይ የተዘረዘሩት አገዛዙ የገባባቸው ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ ቀውሶች በአንድም ይሁን በሌላ መልኩ የህዝቡ የትግል ፍሬዎች ናቸው። ነገር ግን፣ ከፍተኛ ውጤት እያስመዘገበ ያለው የህዝባችን ትግል ለድል እንዲበቃ የሁሉላችንንም ርብርብ ይጠይቃል። በተለይም በውጭ ሀገራት የሚኖሩት ኢትዮጵያዊያን የአገዛዙን ኢኮኖሚያዊ እና ብሎም ፖለቲካዊ አቅም የማንኮታኮት ከፍተኛ ሀይል አላቸው። ኢትዮጵያዊያኑ ወደ ሀገርቤት የሚልኩት ገንዘብ ወይም ሬሚታንስ አገዛዙ በአሁኑ ወቅት በዋነኛነት ተንጠልጥሎ የሚገኝበት ከፍተኛው የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ነው። በዚህ የውጭ ምንዛሬ ምንጭ ላይ በተለያዩ መንገዶች የሚደረግ እቀባ የስረአቱን የኢኮኖሚ ቀውስ በከፍተኛ ሁኔታ የሚያባብስ እና የማፈን አቅሙን የሚያዳክም በኢትዮጵያዊያኑ እጅ ውስጥ ያለ ትልቅ አቅም ነው። በመሆኑም፣ የስርአቱ የኢኮኖሚ ቀውስ ተባብሶ የመግዛት አቅሙ እንዲዳከም እና ብሎም እንዲንኮታኮት እንዲሁም የህዝቡ መስዋእትነት ለድል እንዲበቃ እና የመከራው ጊዜ እንዲያጥር ውጭ ያሉት ኢትዮጵያዊያን ትልቅ ሀላፊነት አለባቸው።
ስለሆነም፣ አለምአቀፍ የኢትዮጵያዊያን የጋራ ግብረሀይል ወደ ህወሓት አካውንት ውስጥ በሬሚታንስ ወይም በሀዋላ መልክ የሚገባው የውጭ ምንዛሬ ላይ እቀባ እንዲደረግ ወገናዊ ጥሪውን ያቀርባል። የህዝባችን የመከራ ጊዜ እንዲያጥር የሚመኝ ኢትዮጵያዊ ሁሉ የሚከተሉትን ጥሪዎች ተግባራዊ እንዲያደርግ ግብረሀይሉ በታላቅ አክብሮት እና በታጋዩ ህዝባችን ስም ጥያቄውን ያቀርባል።
መደበኛ /ፎርማል ቻናል/ በሆኑት እንደ ዌስተርን ዩኒዮን እና መኒ ግራም በመሳሰሉ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች እና ባንኮች አማካኝነት ዶላር፣ ዩሮ፣ ወይም ሌላ የውጭ ገንዘብ እንዳይላክ ግበረሀይሉ ጥሪ ያስተላልፋል። የሚከተሉት የመላኪያ መንገዶች ኢ-መደበኛ ዘዴዎች ሲሆኑ በእነዚህ ዘዴዎች የሚላከው ገንዘብ አገዛዙ አካውንት ውስጥ የመግባት እድሉ በጣም ዝቅተኛ በመሆኑ ህብረተሰቡ በሚኖርበት አካባቢ እያፈላለገ እንዲጠቀምባቸው ግብረሀይሉ በአክብሮት ጥያቄውን ያቀርባል፦
ሀ) በየአካባቢው የሚገኙ ገንዘብ በማስተላለፍ ስራ ላይ የተሰማሩ ነጋዴዎች ወይም ግለሰቦች። ግለሰቦቹ ወይም ነጋዴዎቹ ከወያኔ ጋር ንክኪነት እንደሌላቸው ማረጋገጥ ከተቻለ፣ ይህ ዘዴ በስፋት በስራ ላይ ሊውል ይችላል።
ለ) አገር ቤት ያላቸውን ገንዘብ በተለያየ ምክንያት ወደውጭ ምንዛሬ ቀይረው በውጭ አገራት ማስቀመጥ የሚፈልጉ ሰዎች። የዚህ አይነት ሰዎች በውጭ አገራት ዘመዶች ያሏቸው ሲሆን የገንዘብ ቅያሬውን የሚያከናውኑት በዘመዶቻቸው አማካኝነት ነው።
ሐ) የሚላከውን ገንዘብ ለተጓዦች መስጠት እና ኢትዮጵያ ውስጥ በጥቁር ገበያ መቀየር (የሚቻል ከሆነ ከወያኔ ጋር ንክኪነት ያላቸውን መንዛሪዎች መለዬት)።
መ) እንደ ላፕቶፕ፣ ሴልፎን የመሳሰሉ እቃዎችን ገዝቶ መላክ እና እቃዎቹ ኢትዮጵያ ውስጥ እንዲሸጡ ማድረግ።
ሁኔታዎች ሳይመቻቹ ቀርተው የግድ ዌስተርን ዩኒዮንን በመሳሰሉ የገንዘብ አስተላላፊ ድርጅቶች ገንዘብ መላክ ካስፈለገ፣ የቤተሰቦቻችሁን የኢኮኖሚ ሁኔታ ከግምት ውስጥ በማስገባት የምትልኩትን ገንዘብ መጠን /አማውንት/ ወይም ድግግሞሽ /ፍሪኩየንሲ/ እስከ ሰላሳ በመቶው እንዲቀንስ እንድታደርጉ ግብረሀይሉ በህዝባችን ስም ጥሪውን ያቀርባል።በአገር ቤት ያሉት ቤተሰቦቻችሁ በቂ ገቢ ያላቸው እና ከውጭ የሚላከው ገንዘብ ቢቆም የሚፈጥረው ኢኮኖሚያዊ ጫና ዝቅተኛ ከሆነ፣ የህዝቡን የሞት-ሽረት ትግል ለማገዝ ሲባል ገንዘብ መላካችሁን ለተወሰነ ጊዜ እንድታቆሙ ከታላቅ አክብሮት ጋር ግብረሀይሉ ጥሪውን ያቀርባል።ከስረአቱ ሾልኮ የወጣው የደህንነት ሰነድ እንዳመለከተው እና የኢትዮጵያ ተጨባጭ ሁኔታ እንደሚያሳየው፣ ከሁለት አመት በላይ በዘለቀው ፖለቲካዊ እና ኢኮኖሚያዊ አለመረጋጋት ሳቢያ የገንዘብ ሽሽት ተባብሶ ቀጥሏል። አገርቤት ያሉ ባለሀብቶች ገንዘባቸውን ማሸሽ በጀመሩበት በዚህ ወቅት ለግንባታና ለንግድ በሚል ጠንካራ ገንዘብ /ሃርድ ከረንሲ/ ወደ ኢትዮጵያ ማስገባት ከጥቅሙ ጉዳቱ እንደሚያመዝን በድፍረት መናገር ይቻላል። ለንግድ እና ግንባታ የሚሆን የውጭ ምንዛሬ ወደ ሀገርቤት የምትልኩ ኢትዮጵያዊያን በድካም ያፈራችሁት ንብረታችሁ የተጋረጠበትን አደጋ ከግምት ውስጥ በማስገባት ንግዳቸሁን ወይም ግንባታቸሁን የኢትዮጵያ ሁኔታ እስኪለይለት ድረስ ጋብ እንድታደርጉ ለነጻነቱ በሚዋደቀው ህዝብ ስም ግብረሀይሉ ጥሪውን ያስተላልፋል።

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes