የወገኖቻችን ቁስል የሚሰማው ለእኛ እንጅ ለናዚዎች አይደለም!!!
      
THEY ARE THE REASON!

ነሀሴ 4 ቀን 2009. በአሳዛኝ ሁኔታ ከኢትዮጵያ ወደ የመን ሊሻገሩ የነበሩ ኢትዮጵያዊ ወገኖቻችን ሆን ተብሎ በታጣቂዎች እባህር መወርወራቸውን ESAT እና"VOA" ዘግበዋል፥ ጄኔቫ የሚገኙትን IOM ቢሮ ቃል አቀባይንም አነጋግረዉ ወደ ስፍራው የሚሄድ ልኡካን ቡድን ማዘጋጀታቸውን ገልፀዋል።
ይህ ዓይነቱ ክስተት የመላ ኢትዮጵያዊን ቅስም የሚሰብር እና አንገት የሚያስደፋ ከሀዘንም በላይ ሀዘን ቢሆንም በተለይ በቅርብ ሆነው ባህር የሚተፋውን የወገኖቻቸውን እሬሳ እየጠበቁ በመቅበር ላይ ላሉት ወገኖቻችን ይከብዳል።
ከ180-160 በሚደርሱ ኢትዮጵያውያኖች ላይ የተከሰተ ይህ አደጋ ለናዚዉ ወያኔ ስርዓት  ራዲዮ እና ቴሌቪዥን ግን ለዜና እንኩዋን ብቁ ሆኖ ባለመገኘቱ በግብፅ በባቡር አደጋ ስለሞቱት 41 ሰዎች ነው እያወራ ያለው።
*መንግስት በሌለበት ሐገር ሕዝብ መንግስት ሆኖ መነሳት አለበት!!!
የወገኖቻችን ጥቃት ጥቃታችን ፣ቁስላቸው ቁስላችን ነው፤ሁላችንም የችግሩ ተጠቂዎች ነን
በናዚው ወያኔ ሐገር መነጠቃችን ያመጣብን ጣጣ በየደረስንበት ሞት፣ስቃይ፣ ጉስቁልና ውርደት ብቻ ሆኑዋል።
አንዳንድ የዓለም ሐገራትም ከወያኔ ጋር ባላቸው የጥቅም ትሥሥር ምክንያት በሐገራችን ያለውን የወያኔ አፓርታይድ አገዛዝ ሀጢያትን እየሸፈኑ ከሰዉ በላዉ ሥርዓት ጋር በመቆም ኢትዮጵያ ዲሞክራሲ የተንበሻበሸች ዓይነት አርገው ቢያወሩም ከባህር እና ከየብስ ከየአቅጣጫው የሚሰማው የወገኖቻችን ሰቆቃ ፍንትው አርጎ እውነታውን እያሳየ ነው።

ይህ የወገኖቻችን ከባህር መጣል ወይም በሊቢያ መታረድ ወይም እየታፈኑ መወሰድ በየጊዜው እየደርሰብን ያለ ብሄራዊ ውርደት በመሆኑ ነብስ ይማር ብቻ ብለን ዝም የምንለው ጉዳይ ሳይሆን ኃይላችንን አስተባብረን ይህን ሰው በላ ስርዓት ከስር መስረቱ መንግለን መጣል አለብን!!!
ያን ጊዜ በምድራችን ተከብረን መኖር እንጀምራለን ይህ ሰው በላ ስርዓት ካልተውገደ ግን ቁስላችን በየጊዜው ያመረቅዛል እንጅ አይሽርም ስለዚህ በጋራ ለነፃነታችን እንነሳ።

 
18 ሰዓታት ከተጓዝን በኋላ ባህር ውስጥ ገለበጡን”- ከሞት ከተረፉት መካከል link:- https://amharic.voanews.com/a/yemen-/3982367.html

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes