የኖርዌይ ኦስሎ እኔ ለነፃነቴ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ድጋፍ ዝግጅት
የዘመናት ጠላቶችዋን መክታ ሕልውናዋን ጠብቃ መኖር ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት ሆና ታፍራና ተከብራ የኖረችው ጥንታዊትዋ ሐገራችን ዛሬ በደደቢት በረሐ ከውስጥዋ የበቀሉ የእናት ጡት ነካሾች እንደ ሐገር የመቀጠል ሕልውናዋን እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመጣል የሕዝቡን መከራና ስቃይ እስር እና እንግልት በማብዛት አይቀጡ ቅጣት እየቀጡ ጣሩን ያበዙበት ሕዝባችን ከዳር እስከዳር በቃኝ ፤ሰለቸኝ ብሎ በመነሳት ለነፃነት የሚከፈለውን መስዋትነት ሁሉ እየከፈለ ወያኔን አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል።

ይህ ዙሪያ ገባውን እንቢ፣በቃኝ፣ሰለቸኝ ብሎ በተነሳ የሕዝብ አመፅ ከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ፋሺስቱ ወያኔ ከመቃብር አፋፍ ላይ ሆኖም እንኩዋ ከአያት ቅድማያቶቹ  የወረሰውን ኢትዮጵያን የማፍረስ ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ ሐገር እያቃጠለ ፤ንብረት እያወደመ፣ ኢትዮጵያ ሐገራችንን ዙሪያ ገባዋን እየሸጠ በሕዝብ ላይ አፈናውን አጠናክሮ በቃላት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍተኛ ግፍና በደል እየፈፀመ ይገኛል።

ተፈጥሮ የቸረችውን የመናገርና የመተንፈስ መብቱን ተነፍጎ ለከፍተኛ መከራ፣ስቃይ ፣እንግልት እና ስደት የተዳረገው ሕዝባችን ግን እየታሰረም፣እየተገደለም፣እየተሰቃየም "እምቢ ለሐገሬ እምቢ ለነፃነቴ" በማለት ባንዳውን ወያኔ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ የኢትዮጵያን ትንሳኤ ለማብሰር በገንዘብ ለማይተመን ሕይወቱ ሳይሳሳ ብዙኃኑ ከወያኔ ጋር ጉሮሮ ለጉሮሮ እየተናነቀ ባለበት በዚህ ፈታኝ ወቅት ወደ ወሳኝ የትግል ምእራፍ ላይ እየተሸጋገረ የሚገኘው ለአንድነትና ለዲሞክራሲ የሚደረግ ትግል ከምን ጊዜውም በላይ የሚያስከፍለው ዋጋ በመጨመሩ ብዙ የነፃነት አርበኞች ወያኔን አስወግዶ ነፃነት፣ፍትሕ እና እኩልነት የሰፈነበትን ስርዓት ለመመስረት በሚደረገው ትግል የመጨረሻውን የሕይወት መስዋዕትነት እየከፈሉ በሚገኙበት በዚህ እጅግ ፈታኝ እና አማራጭ በሌለው ትግል ውስጥ የሕዝቡን ትግል በማስተባበር እና በመምራት የሚቻለውን ሁሉ እያደረገ የሚገኘው የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በየሐገሩ ተበትነው ያሉ ሐገር ወዳድ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ለነፃነት እየተዋደቁ ላሉት አርበኞቻችን ለትግሉ ያላቸውን አጋርነት እና ሙሉ ድጋፍ ሊገልፁ የሚችሉበት በመላው ዓለም በሚገኙ 30 በላይ በሆኑ ከተሞች በፌብሮዋሪ 11 እና 12/2017 የሚካሄድ እኔ ለነፃነቴ ዓለም አቀፍ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ድጋፍ ዝግጅት አዘጋጅቱዋል ።
 በዚህ ፕሮግራም መርሐ ግብር መሰረት:-
እኔ ለነፃነቴ የሚለውን መሪ ቃል በመያዝ  በኖርዌይ ያለው ኢትዮጵያዊ  ሁሉ ሊሳተፍ እና ትግሉ የሚጠይቀውን አስተዋፅዖ ሊያደርግ የሚችልበትን  ትልቅ የድጋፍ እና የውይይት መድረክ ለማዘጋጀት ግብረ ኃይል አቁዋቁሞ ከፍተኛ እንቅስቃሴ በማድረግ ላይ የሚገኘው ኖርዌይ የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ በአሁኑ ሰዓት ዝግጅቱን አጠናቆ ታዳሚዎቹን በመጠባበቅ ላይ መሆኑን የደረሱን መረጃዎች ይጠቁማሉ።
 
በግብረ ኃይሉ መርሃ ግብር መሰረት ፌብርዋሪ 11.2017 . 2 pm ጀምሮ በሚካሄደው እኔ ለነፃነቴ ዓለም አቀፍ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ድጋፍ ዝግጅት ላይ የድርጅቱ ከፍተኛ አመራር አቶ ደባሱ መሰሉ በአካል እንደሚገኙና የአርበኞች ግንቦት 7 ንቅናቄ ሊቀመንበርም ፕሮፌሰር ብርሐኑ ነጋ ኢትዮጵያ ውስጥ ስላለው አጠቃላይ የትግል እንቅስቃሴ ሰፊ ማብራሪያ እና ለሚጠየቁ ጥያቄዎች ከበረሐ በስካይፕ መልስ እንደሚሰጡ ተገልፅዋል።
በፋሺስቱ ወያኔ አደጋ ላይ የወደቀውን የሐገራችንን ሕልውና ለመታደግ እና በሕዝባችን ላይ የተጫነውን የመከራ ቀንበር ሰብሮ ለመጣል ብዙዎች እየተዋደቁ ባለበት በዚህ ወሳኝ ወቅት በተዘጋጀው ታላቅ ዝግጅት ላይ በአካል ሜዳ ድረስ በመሳተፍ ባለን አቅም ሁሉ የትግሉ አጋር መሆናችንን ለአርበኞቻችን  የምናሳይበት  ዝግጅት በመሆኑ  እርሶም ይጠቅማል፣ ይበጃል ያሉትን ሐሳብ ይዘው የፕሮግራማችን ታዳሚ ይሁኑ ሲልም  የዚሁ ኖርዌይ እኔ ለነፃነቴ ሕዝባዊ ውይይት አዘጋጅ ግብረ ኃይል በኖርዌይ ለሚገኘው ኢትዮጵያዊ ማሕበረሰብ እና ትውልደ ኢትዮጵያውያን በሙሉ ጥሪውን  ያስተላለፈ ሲሆን
ፕሮግራሙ መርሀ ግብር መሰረት የሎተሪ፣ የጨረታ እና ሌሎች የተለያዩ መርሀ ግብሮች እንዲሁም ምግብ ና መጠጥ ዝግጅት እንዳለም ተገልፁዋል።
 

Comments

Popular posts from this blog

Addis standard’s exclusive interview with Ana Gomes