Posts

Showing posts from February, 2017
Image
                                                           ሐገሬ ! ሐገሬ!                የጠላሽ ይጠላ፤ከምድረ ገፅ ይጥፋ፣                  መዋቢያ ክብር ነሽ ፤የብዙዎች ተስፋ።                  ሐገሬ ሐገሬ ፣                 መመኪያዬ ክብሬ።                 ስሚኝ እናት ዓለም፤እስኪ ልጠይቅሽ፣                 ስንት አራሙቻዎች በውስጥሽ አብቅለሽ፣                 ትኖሪብናለሽ አኬል ዳማ ሆነሽ።                 በቃ!በቃ! በይ እማማ አንቅረሽ ትፊያቸው፣                 ከጉያሽ ፈልቅቀሽ አውጥተሽ ጣያቸው።                 ስንት ጊዜ ይካዱሽ ፣?                 ስንቴስ ይቅጠፉብሽ፣?                 ያልተፃፈ ታሪክ እያነበቡብሽ።                 እኒህ የማይረቡ የእንግዴ ልጆችሽ፣                 ስንት ጊዜ ይካዱሽ ?                ስንቴስ ይቅጠፉብሽ?
Image
የኖርዌይ ኦስሎ እኔ ለነፃነቴ የአንድነት እና የዲሞክራሲ ድጋፍ ዝግጅት የዘመናት ጠላቶችዋን መክታ ሕልውናዋን ጠብቃ መኖር ብቻ ሳይሆን የመላው ጥቁር ሕዝብ የነፃነት ተምሳሌት ሆና ታፍራና ተከብራ የኖረችው ጥንታዊትዋ ሐገራችን ዛሬ በደደቢት በረሐ ከውስጥዋ የበቀሉ የእናት ጡት ነካሾች እንደ ሐገር የመቀጠል ሕልውናዋን እጅግ አሳሳቢ ደረጃ ላይ በመጣል የሕዝቡን መከራና ስቃይ እስር እና እንግልት በማብዛት አይቀጡ ቅጣት እየቀጡ ጣሩን ያበዙበት ሕዝባችን ከዳር እስከዳር በቃኝ ፤ሰለቸኝ ብሎ በመነሳት ለነፃነት የሚከፈለውን መስዋትነት ሁሉ እየከፈለ ወያኔን አጣብቂኝ ውስጥ ከቶታል። ይህ ዙሪያ ገባውን እንቢ፣በቃኝ፣ሰለቸኝ ብሎ በተነሳ የሕዝብ አመፅ ከፍተኛ አጣብቂኝ ውስጥ የገባው ፋሺስቱ ወያኔ ከመቃብር አፋፍ ላይ ሆኖም እንኩዋ ከአያት ቅድማያቶቹ   የወረሰውን ኢትዮጵያን የማፍረስ ተልዕኮ ተግባራዊ ለማድረግ ሐገር እያቃጠለ ፤ንብረት እያወደመ፣ ኢትዮጵያ ሐገራችንን ዙሪያ ገባዋን እየሸጠ በሕዝብ ላይ አፈናውን አጠናክሮ በቃላት ተዘርዝሮ የማያልቅ ከፍተኛ ግፍና በደል እየፈፀመ ይገኛል። ተፈጥሮ የቸረችውን የመናገርና የመተንፈስ መብቱን ተነፍጎ ለከፍተኛ መከራ፣ስቃይ ፣እንግልት እና ስደት የተዳረገው ሕዝባችን ግን እየታሰረም፣እየተገደለም፣እየተሰቃየም " እምቢ ለሐገሬ ፤ እምቢ ለነፃነቴ " በማለት ባንዳውን ወያኔ አይቀጡ ቅጣት ቀጥቶ የኢትዮጵያን ትንሳኤ ለማብሰር በገንዘብ ለማይተመን ሕይወቱ ሳይሳሳ